Amharic Translations Archive

በፕሮፌሰር መስፍን “አዳፍኔ“ መጽሐፍ ላይ አንዳንድ የሀሳብ ፍንጣቂዎች፡ ኢትዮጵያውያንን ከእራሳቸው መጠበቅ?

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ አሁን ከቅርብ ጊዜ በፊት “አዳፍኔ፡ ፍርሀት እና መክሸፍ እንደ ኢትዮጵያ“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀው እና ታትሞ የወጣው የፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም የአማርኛ መጽሐፍ የኢትዮጵያ ህዝቦች በብልሹ አስተዳደር፣ በአምባገነናዊነት የጭቆና አገዛዝ እና በሞራል ስብዕና መብከት ምክንያት ተዘፍቀው ከሚገኙበት የኃጢአት ባህር ውስጥ እራሳቸውን በንስሀ በማደስ ከሀጢአት እንዲጸዱ የማያዳግም እርምጃ እንዲወስዱ የሚያሳስብ ነው፡፡ ፕሮፌሰር

ሌላ ደብዳቤ ለኢትዮጵያውያት እህቶቼ፣

በምስራቅ ገሰሰ  በአሁኑ ጊዜ ይህንን ደብዳቤ እየጻፍኩ ያለሁት ለጡት ካንሰር በሽታ ምርመራ አስፈላጊ የሆኑትን የኤክስ ሬይ/X-Ray እና የአልትራ ሳውንድ/Ultrasound ዓመታዊ ምርመራዬን እንዳጠናቀቅሁ ነው፡፡ ከአምስት ዓመታት በፊት ልክ እ.ኤ.አ መስከረም 25/2010 የጡት ካንሰር ምርመራዬን ካጠናቀቅሁ በኋላ ለኢትዮጵያውያት እህቶቼ ይጠቅማል በሚል እሳቤ ከዚህ ጋር በተያያዘ መልኩ ያለኝን ልምድ እና ተሞክሮ ያካተተ ጽሑፍ አዘጋጅቼ ነበር፡፡ (ያንን ጽሑፍ በእንግሊዘኛ  ለማንበብ እባክዎትን

ዘ-ህወሀት በኢትዮጵያ የተከሰተውን ረሀብ ማቆም ይችላልን?

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም     ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ   ኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ በአውዳሚ ረሀብ መካከል ተሰንጋ መያዟ ታላቅ ዓለም አቀፍ ሚስጥር ሆኖ ይገኛል፡፡ እ.ኤ.አ ከ1984-85 ወዲህ ለሁለተኛ ጊዜ የተከሰተ ታላቅ ረሀብ! ባለፈው ሳምንት ግሎባል ፖስት/Global Post የተባለው የዜና ወኪል በርዕሰ አንቀጹ የመጀመሪያ ርዕስ በማድረግ እንዲህ የሚል ጥያቄ አቅርቧል፡ “ኢትዮጵያ ባለፉት 30 ዓመታት ጊዜ ውስጥ በአስከፊነቱ የመጀመሪያ የሆነውን ድርቅ ተጋፍጣ

የስደት መንግስት ለኢትዮጵያ?

ከፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም     ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ መግቢያ ከጥቂት ሳምንታት በፊት ስለ የስደት መንግስት መስፈርት በዓለም አቀፍ ሕግ መሰረት ለአንድ የኢትዮጵያ የሲቪክ ማህበረሰብ ቡድን ቃለ መጠይቅ ሰጥቸ ነበር፡፡ ስለስደት መንግስት ጽንሰ ሀሳብ እና ስላለው ተሞክሮ ዓለም አቀፍ ዕውቅና ያለው ወይም የሌለው ስለመሆኑ ያለኝን አስተያየት እንድሰጥ ተጠይቄ ነበር፡፡ ቀጥታ ያልሆነው እና ዘወር ያለው ጥያቄ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ምድር ላይ ነግሶ በሚገኘው

ፕሬዚደንት ሬጋን ሲያራምዱት በነበረው በስደተኝነት እና በፖለቲካ ጥገኝነት ፖሊሲ ላይ ትክክል ነበሩን?

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም     ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ስለሬፐብሊካኖች እና ስለሚያራምዷቸው ድምጸቶች ስናገር ቆይቻለሁ፡፡ አንዳንዶች በሬፐብሊካኖች እና በሬፐብሊካን ፓርቲ ላይ ከፍተኛ የሆነ ንዴት ያደረብኝ እንደሆነ አድርገው ሊገምቱ ይችላሉ፡፡ እኔ ስለእዚህ ጉዳይ ብዙም አልጨነቅም፡፡ ይልቁንም ከዚያ በበለጠ መልኩ በመጋዘኔ ውስጥ የ”ዴሞክራሲ አይጦች” አገዛዝ ተንሰራፍቶ ይገኛል፡፡ ሆኖም ግን በአሁኑ ጊዜ ለዕጩ ፕሬዚዳንታዊነት ምርጫ በመወዳደር ወደ ኋይት ሀውስ ለመግባት አሰፍስፈው

ኢትዮጵያ እንደ ጋና መሆን የማትችለው ለምንድን ነው?

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም     ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ በአደባባይ በይፋ አምናለሁ፡፡ በጋናውያን ላይ መንፈሳዊ ቅናት አድሮብኛል፡፡ ባራክ ኦባማ የመጀመሪያ ጉዞውን ወደ አፍሪካ ባደረገበት ወቅት በአፍሪካ ከፍተኛ የህዝብ ቁጥር ወዳላት እና የከፍተኛ የምጣኔ ሀብት ባለቤት ወደሆነችው ወደ ናይጀሪያ ለመሄድ አልመረጠም፡፡ በአሁጉሩ በምጣኔ ሀብት ደረጃዋ የሁለተኛነት ደረጃ ወደያዘችው የኔልሰን ማንዴላ ሀገር ደቡብ አፍሪካ ለመሄድ አልመረጠም፡፡ እንደዚሁም ደግሞ ኦባማ የወላጅ አባቱ የትውልድ ሀገር

ረሃብ በኢትዮጵያ በባቡር ይጋልባል፣

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም     ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ የኢትዮጵያ ዓመታዊ የረሃብ አዝመራ፣ ባለጥቁሩ ፈረስ የረሃብ የምጽዓት ቀን አስፈሪውን ፊቱን በኢትዮጵያ እንደገና ማሳየት ጀመረ፡፡ በአሁኑ ጊዜ በባቡር ተቀምጦ በመጋለብ ላይ ይገኛል፡፡ እ.ኤ.አ የካቲት 2014 በዚሁ ወር ኤንቢሲ/NBC የተባለ ዓለም አቀፍ ድርጅት ያወጣውን የምርመራ ዘገባ መሰረት በማድረግ “እየተንፏቀቀ የመጣው ረሃብ በኢትዮጵያ “ በሚል ርዕስ ትችት አቅርቤ ነበር፡፡ በዚያን ጊዜ ኤንቢሲ/NBC እንዲህ የሚል

የግል ደብዳቤ፡ ይድረስ ለሴናተር ቴድ ክሩዝ 

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም     ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ  ለተግባራዊ  ድርጊት የቀረበ ጥሪ፣ ልዩ ምልከታ እና ጥያቄ፡ በዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ የምትገኙት አንባቢዎቼ በተለይም ደግሞ በታላቁ የቴክሳስ ግዛት እና በዋሽንግተን ዲሲ ሜትሮፖሊ አካባቢ የምትኖሩ ኢትዮ-አሜሪካውያን በሙሉ በኢትዮጵያ የዩናይትድ ስቴትሰ አሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (ዩኤስኤአይዲ)/United States Agency for International Development እየተባለ የሚጠራውን ዓለም አቀፍ ድርጅት በበላይነት እንድትመራው ለሹመት የተጠቆመችውን ጋይሌ ስሚዝን በመቃወም

ኢትዮጵያ የተሻሉ አማራጮችን አጥታ ነውን ?

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም       ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ እ.ኤ.አ ግንቦት 2015 “ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ የእራሱን ጥላ የሚፈራው ለምንድን ነው?“ በሚል ርዕስ ትችት አቅርቤ ነበር፡፡ በዚያ ትችት ላይ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ደጋፊዎች የወያኔው አመራሮች በግንቦት ስለሚካሄደው የይስሙላ የቅርጫ ምርጫ በፍርሀት ቆፈን ውስጥ ተሸብበው የመገኘታውን እውነታ ሲነግሩኝ ለእኔ ይህ ሁኔታ በጣም እንቆቅልሽ እንደሆነብኝ ግልጽ አድርጌ ነበር፡፡ የተሰማኝን አግራሞት

ቴዲ “የፍቅር ነብዩ”ን ተውት ስለ ፍቅር ደግሞ ደጋግሞ ይዘምር…

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም     ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ እረ ተዉኝ ባትነኩኝ ምናለበት አባካችሁ ሰዎች ስራዬን ልስራበት። ታላቁ ጥላሁን ገሠሠ         ፍቅር ሁሉንም ድል ያደርጋል ! ሸክስፒር “አስራሁለተኛው ሌሊት“ በሚለው የትያትር ፁሁፋቸው ላይ የኦርሲኖ መስፍን በአዳራሹ ተሰባስበው ለነበሩት ድምጻውያንና ሙዚቀኞች  እንዲህ በማለት ተናግረው ነበር፣ “ሙዚቃ የፍቅር ምግብ እስከሆነ ድረስ አሁንም ዘምሩ፣ በርካታ ሙዚቃዎችን ደግማችሁ ደጋግማችሁ ዘምሩልኝ…“ እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) እያለ የሚጠራው የወያኔ