እሪ! እንበል ለኢትዮጵያ (ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም)

ከፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም ከነጻነት ለሃገሬ

Click here for PDF

ለመናገር ነጻነት

የቆየውን አበባል ለማስታወስ፤‹‹በማንኛውም ሕብረተ ሰብ ውስጥ እጅጉን አስፈላጊ የሆኑ ሁለት ጉዳዮች ይገኛሉ፡፡ የመጀመርያው በነጻነት መናገር ሲሆን ሌላውን ግን አላስታውሰውም›› ይባላል::

በነጻነት መናገር የሁሉም የሰብአዊ መብቶች መሰረት ነው፡፡ በኔ ግምት፤የህብረተሰቡ ሃሳብን የመናገርን ነጻነት የሚሰጠው ዋጋ፤ ያ ሕብረተሰብ ነጻ መሆን አለመሆኑን  የሚያረጋግጥበትEthiopian flag መንገድ ነው፡፡ ግለሰቦች ያሻቸውን ለመናገር ፍርሃት ካደረባቸው፤ እንደህሊናቸው ፈቃድ ማሰብ፤ መጻፍ አለያም መንግስትን  በመፍራት ከፈጠራ ተግባራቸው ከተገደቡ፤ ሊደርስባቸው በሚችል ማስፈራሪያና ዛቻ ወከባና እስር በመፍራት ያሰቡትን ማድረግ ካልቻሉ፤ያ ህብረተሰብ ነጻነቱን የተሰለበ ይሆናል:: ሃሳብን በነጻነት የማንሸራሸር መብት በአሜሪካን ሪፓብሊክ አመሰራረት ላይ ግዙፍ ቦታ ሊኖረው ስለተገባ፤ አሜሪካን የመሰረቱት ጨርሶ ሊነካ፤ ሊቀለበስና ልዩ ትርጉም ሊሰጠው የማይችል መሰረቱ የጸና ሕገ መንግስታዊ ድጋፍና ከለላ አደረጉለት፡፡ በዚህም ላይ በመመስረትና በእንግሊዝኛው ቋንቋ አማራጭ ትርጉም እንዳይኖረው በማድረግ ‹‹ኮንግሬስ በምንም መልኩ ቢሆን የመናገር ነጻነትን በሚጥስ መልኩ፤ወይም የፕሬስን መብት የሚገድብ ማንኛውንም ሕግ ሊያወጣ አይችልም›› በማለት ደምድመው አስከመጡት፡፡

በማንኛውም ሕብረተሰብ ውስጥ የመናገር ነጻነትን ለማክበርና ለመጠበቅ የሚያስፈልጉበት በርካታ ምክንያቶች አሉ፡፡ የመናገር ነጻነት በሌለበት ሰዎች እንደተወተፈ ጠርሙስ ናቸው፡፡ግንኙነት የላቸውም፤ሃሳባቸውን ማንሸራሸር አይችሉም፤ስለፖለቲካ ያላቸውን አመለካከት፤ስለምንግስትና መንግስት ስለሚያወጣቸው ፖሊሲዎች ስሜታቸውንና ሃሳባቸውን መሰንዘር አይችሉም፡፡ መሪዎችና ገዢዎች ላይ ሂስ መሰንዘር አለያም ተጠያቂ ማድረግም አይቻልም ምክንያቱም ሃሳብን በነጻ መግለጽ ወንጀል በመሆኑ ነው፡፡ ለጥበባዊ፤ለቋንቋ እድገት ወይም ለበሰለ አስተሳሰብ ማንሸራሸሪያ በጣም ውስን ቦታ በመኖሩ በሕብረተሰቡ ውስጥ ስላሉት ከፍተኛ ጉዳዮች ለማንሳትና ለመወያየት ያለው ቦታ ጠባብ ይሆናል፡፡ በአጭሩ፤የመናገር ነጻነት በሌለበት፤ ‹‹እድገት ይሰነከላል፤የህብረተሰብ ሁኔታ መሻሻል ባለህበት ሂድ ይሆንና ብቸናው የእውነት መንገድ የገዚዎች ቅጥፈት ወደ እውነትነት ይለወጣል፡፡

የማያጠያይቀውን የመናገር መብት በተመለከተ ለመጻፍ አይደለም አነሳሴ፡፡ ወይም የመንግስታትን የመናገር መብት መጣስ ለመወንጀልም አይደለም የዛሬው አላማዬ፡፡ በርካታ አንባቢዎቼ የመናገር ነጻነትን መብትና ሌሎችም ሰብአዊ መብቶች በተመለከተ በምንም መልኩ ሊተካ የማይችል የመከራከርና ተግባራዊ የሚደረግበትን ሁሉ ለማረጋገጥ እንደምሟገት አበክረው ያውቁልኛል፡፡ በ2010 ፈላጭ ቆራጩ አምባገነን የግፍ ገዢ መለስ ዜናዊ፤በኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ ለማናግር በመጣበት ወቅት፤የሱንም የመናገር መብቱ እንዲከበር ተሟግቼላታለሁ፡፡ በዚህም ከወዳጅ ጓደኞች የሰላ ወቀሳና ሂስ ደርሶብኛል፡፡ ሆኖም ግን ምንም ያህል መለስ ዜናዊን በእኩይ ባሕሪው ብወቅስና ብኮንነውም፤ስለተግባሩ አስተያየት የሚሰጡትን ሁሉ እንደጠላት በመመልከት ለስቃይና ለእንግልት ቢዳርግም፤ሃገሪቱን ወደአዘቅት እንደሚጥል ባውቅና ያንንም ብቃወመውም፤በሃገሪቱ ያሉትን መገናኛዎች ሁሉ አፍኖ ቢይዝም፤የአሜሪካን ድምጽንና ነጻውን የሳታላይት ቴሌቪዥን ቢያግድና እኔም ብኮንነው፤በኮሎምቢያ ዩኒቨርስቲ ተገኝቶ ንግግር የማድረግ የነጻነት መብቱን ግን እጠብቅለታለሁ፡፡ አዎንና መለስ ዜናዊ ጋዜጠኞችን ለእስር በመዳረግ በአፍሪካ ሁለተኛው ደረጃ ላይ ያለው እኩዩ አረመኔው መለስ ዜናዊ በነጻ ሃሳቡን የመነግለጽ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ባለፈው ጃንዋሪ ላይ የጁንታው መሪ የፈላጭ ቆራጩ መንግስቱ ሃይለማርያም መጽሃፍ የኮፒ ራይትን ህግጋት በጣሰ መልኩ ኮፒ ሲደረግና በየድህረገጹ ላይ ሲለጠፍና መንግስቱ ነፍሰ ገዳይ በመሆኑ፤ ሕዝብን ለመከራና ለሰቆቃ የዳረገ በመሆኑ፤ ያለአንዳች ርህራሄ ሕዝብን የጨፈጨፈ በመሆኑና ላደረሰው በደልና ለፈጸመው ኢሰብአዊ ድርጊት ዋጋገውን አልከፈለምና ከዚህ መጽኃፉ ሽያጭ ጥቅም ሊያገኝ አይገባውም ሲባል ያን ጊዜም ቢሆን፤ ምንም ያህል እብለትና ቅጥፈት የተሞላበት መጵሃፍ ቢሆም  ሃሳብን የመግጽ መብቱ ሊጠበቅለት እንደሚገባ ተናገሬያለሁ፡፡

የእነዚህን ሁለት አረመኔ የጥፋት መንትዮች ጨካኝ ውጉዝ ከመአርዮስ ገዢዎች ሃሳብን በነጻ የመግለጽ መብታቸውን ስሞግትላቸው፤ በይበልጥ የሞገትኩት ግን አማራጭ የሌለውን የማንኛውን ሰብአዊ ፍጡር ሃሳብን በነጻ ለመግለጽ መብት ነው የቆምኩት፡፡ በነጻ የመናገር መብት፤በነጻ የመናገርም ያለመናገርም የሁለቱም መብት ማለት ነው፡፡የሌሎችንም ለማዳመጥና በሌሎችም ለመደመጥ ወይ አለማዳመጥና አለመደመጥ መብት ነው፡፡ ይህ የያንዳንዱ ግለሰብ ምርጫ ነው፡፡ በሃሳብ ከማልስማማቸውም ሰዎች ጋር መነጋገርንና ሃሳበቸውን ማድመጥ ባህሪዬ ነው፡፡ በሃሳብ ልዩነት ላይ ቆመን መደማመጥ ግዴታ ነው፡፡ ያንድን ሰው ሃሳብ ለመቃወምም ሆነ ለመደገፍ ማድመጥ ያስፈልጋል::  በሃሳብ ለመስማማትም ላለመስማማትም መወስን የምችለው የሌላውን ሃሳብ ሰምቼ እንነጂ በጭፍን መወሰን ያስቸግራል፡፡ በሃሳባቸው ካልተስማማሁ ምክንያቱን አብጠርጥሬ ማወቅና ማሳወቅም ይገባኛል፡፡ የሌሎችን ሃሳብ ውድቅ ከማደረግ በፊት ማድመጥ አስፈላጊ ነው፡፡ የማንንም ሃሳብ ስቃወም ምክንያቱን ቁልጭ ባለ መልኩ አስቀምጬና አስረድቼ ነው፡፡ ስምምነትም ላይ ሆነ መለያየት ላይ ለመድረስ ሃሳብን ማድመጥ አስፈላጊ ነው ካልሆነ በጭፍኑ የሚደረግ ተቃውሞ ምክንያተ ቢስ ሊያደርገን ይችላልና፡፡

ከዚህ ባልተናነሰ መልኩ ሃሳብን በነጻ የመግለጽ መብት ሊከበር የሚገባበት ሌላም ምክንያት አለ፡፡ የራሴ የመደምደሚያ ሃሳብ ላይ ለመድረስ እንደመፈለጌ ሁላ፤ሌሎችም ወደራሳቸው መደምደሚያ ሃሳብ እንዲደርሱ ፍላጎትና ፈቃደኝነት አለኝ፡፡ መንግስቱንና መለስን የሚደግፉን የሚያምኑባቸውም አሉ፡፡እነዚህ ተባባሪዎቻቸው፤ ያለምንም ጥያቄ የመሪዎቻቸውን ሃሳብ የማድመጥ መብት አላቸው፡፡ ሌሎችችንም እውነታቸውንም ሆነ ቅጥፈታቸውን ያለማዳመጥ መብት አለን፡፡ አድምጠናቸው ሌላ አሳማኝ አማራጭም ሆነ ሂስ ልናቀርብላቸው ልንመርጥም እንችላለን፡፡ ነጻ የመናገር መብት፤በ‹‹እውነት›› ላይ ማንም የሞኖፖል መብት ሊኖረው እንደሚችል አልተደነገገም፡፡ ሁሉም ፍጡሮች እኩል መፈጠራቸውንና በህይወትም ላይ ያልተዛባ ሰብአዊ ጉዳዮች አሉት በሚለው የማያልፉና የማይሞቱ ዘልዓለማዊ እውነታዎች እንዳሉ ብገነዘብም፤መሪዎች ስልጣናቸውን የሚያገኙትም ከሚያስተዳድሩት ሕብረተሰብ ነጻነትና  ፍካጎት የሚወጣ እንደሆነ እገነዘባለሁ፡፡

ማንም ቢሆን  ሞራላዊ የበላይነትን በመቀዳጀት፤በሚሊዮን የሚቀጠሩ ዜጎችን በመጨፍቸፍ ለስላጥን ከበቃው ላይ በመውሰድ መልሰው ለመጨፍጨፍ ቂም በቀል መሰለፍ እንደማይገባቸው አምናለሁ፡፡ተቃዋሚ ሃሳብ ያላቸውን በማፈን የነጻ ሃሳብን የመግለጽ መብት ደጋፊ ነኝ ማለት አይችልም፡፡ ‹‹የምንቃወማቸውን አካላት ሃሳብ ለማድመጥ ፍቃደኝነት ከጎደለን በነጻ የንግግር መብትም ጨርሶ አናምንም ማለት ነው››ይላል ኖአም ቾምስኪ፡፡ እንዲያውም የምንቃወማቸው አካላት ግልባጭ እንሆናለን፡፡

 መናገርም መጻፍም የተነፈጉ

ከላይ የተነሱት መከራከሪያዎች ሁሉ ምክንያታቸው የመናገር ገደብ የተጣለባቸውን ወይም በራሳቸው እራሳቸውን የገደቡትን በይፋ እንዲናገሩና እንዲጽፉም ለማነሳሳት ነው፡፡ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያዊ ያለሆኑት ምሁራን ሁሉ፤ የኢትዮጵያን ሕብረተሰብ በተያየ መንገድ ሲያጠኑ የቆዩ አሉ፡፡ ይሁንና እነዚህ ምሁራን የኢትዮጵያ ከፍተኛ ጉዳይ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ለመተንፈስም ለመጻፍም አልፈለጉም ወይም አልደፈሩም፡፡በሃገር ውስጥ ያሉት ምሁራን ግን በገዢው መደብ እስር እንግልት፤ ከስራ መባረር፤ ወደ እስር መጣልን በመፍራትና በመሸሽ ከመጻፍ ተቆጥበዋል፡፡ ከርቀት በሚሰነዘር የሳንሱር ፍራቻም ሳቢያ የዲያስፖራውም ምሁሮች አይጽፉም፡፡አሁን በስልጣን ካለው የአመለካከት ፍልስፍና አለያም የአመለካከት ልዩነት አንስተው ቢጽፉ ዘለፋና ውርጅብኝ ይደርስብናል በሚል ስጋት ዝም ብለው ተመልካች ሆነዋል፡፡ ፖለቲካውየተሳሳተ መሆኑን ቢናገሩ ጣጣ ይከተላቸዋል፤በማንኛውም የፖለቲካ ስብሰባ ላይ ተቃውሞ ቢያነሱና ሙግት ለመግጠም ቢሞክሩ፤አለያም ስህተቱን አንስተው ትክክለኛውን መንገድ ቢጠቁሙ በበነገታው ስማቸው ጭቃ ለጭቃ ሲጎተትና ክብራቸው ሲደፈር ይታያቸውና ይተዉታል፡፡ በዚህና በመሳሰሉት ሰበቦች ስለ ኢትዮጵያ ለዘመናት ጥናት ያካሄዱና እውቀቱና ችሎቱ የተረፋቸው ምሁራን ከጉዳዩ ጨርሰው እራሳቸውን በማግለል ተመልካችነትንና አድማጭነትን መርጠዋል፡፡

ሁሉም ኢትዮጵያን ሲያጠኑና ስለ ኢትዮጵያ እውቀት ያዳበሩት ሁሉ አሁን ጊዜያዊው ጥሪ አስፈላጊነታቸውን ይጣራል፡፡ለዝምታና ለተመልካችነት፤ለምን አገባኝና፤ ጊዜው ሲመጣ ማለትን ትተው አሁን ነው በራሳቸው ላይ የጣሉትን የዴሞክራሲ ገደብ ወዲያ ጥለው አሁን ኢትዮጵያ የሚያስፈልጋትን ከፈላጭ ቆራጭ አገዛዝና ከጥቂቶች የሰቆቃ ዘመን መገላገያውን በሰላማዊ መንገድ ለማምጣት መሰለፍ ያለባቸው፡፡ ዛሬ ኢትዮጵያ በመስቀልኛው መንገድ ላይ ቆማለች፡፡ የለውጥ ምልክቱም ቁልጭ ብሎ እየታየ ነው፡፡የነጻነትና የዴሞክራሲ ማለዳ ጸሃይም ፈላጭ ቆራጭነትንና ማን አለብኝነትን በዚህ ጸሃይ ቀልጠው ሊጠፉ ነው፡፡ የግፈኛ ገዢዎችም መኩራራትና ድንፋታ የመጨረሻው ጠርዝ ላይ ደርሶ በመንገዳገድ ላይ ነው፡፡ የትዮጵያውያን ፈላጭ ቆራጭ ጨካኝ ፈላጭ ግፈኛ ገዢዎች የመፈንደቂያ ዘመን ወደማክተሙ ነው፡፡ የነጻነት ጎዳናዎች ሁሉ በመዝጋት ሊያፍኑና አሁንም መልሰው ለመግዛት ተስፋ በማድረግ ይንደፋደፋሉ፡፡ አሁን የነጻነት ፈላጊው ሕዝብ የነጻነት ሙዚቃ እየጮኸባቸው ነው፡፡ አሁን የጋንዲ መልእክት እየተሰማቸው ነው– “ግፈኞችና ነፍሰገዳዮች ነበሩ፤ለጊዜው የማይደፈሩ ቢመስሉም ውለው አድረው ግን አይወድቁ ውድቀት ወድቀው አይቀሉ ቅሌት እንደሚከናነቡ የተረጋገጠ ነው›› እስቲ ደጋግማችሁ አስቡት::

በመጨረሻው ሰአት ላይ እነዚህ አረመኔ የሕዝብ ጠላቶች ሲጨንቃቸውና ግራ ሲገባቸው የመጨረሻውን መሳሪያቸውን ሊመዙ መጣራቸው አይቀርም፡፡የመቸረሻው ማጣፊያው ሲያጥርባቸው በየቦታው እሳት መጫር፤ ንዳድ ማስነሳታቸው አይቀርም: እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይበቀል እንዲሉ፡፡እዚህ ላይ ግን እሳትና ንዳድ ለይቶ እንደማያቀጥል ነው፡፡ይህን አድርግ ይህን እሰር፤ይህን ፍጠር ሊሉት እንደማይችሉ መገንዘብ ይሳናቸዋል፡፡ ያገኘውን ሁሉ እያቃጠለና እያጠፋ እንደሚጓዝም አላወቁም፡፡

እነዚህ ሁሉ ለሕዝቡ ተስፋ የሰነቁ ቀናት ናቸው፡፡ በጭፍን ጨካኝ አረመኔ ገዢዎች የመጨረሻ የጥፋት ፍንጣቂ ጠርዝ ላይ የነጻነት ተስፋ ብርሃን ሲፈነጥቅ ያታያልና፡፡ የዴሞክራሲ፤ የሰብአዊ መብት፤የሕግ የበላይነት የብርሃን ጨረር ወደሕዝቡ አቅጣጫ ያበራል፡፡ ሕዝቦች አረመኔ ገዢዎችን መፍሪያ ዘመኑ አብቅቷል:: አረመኔ ገዢዎች በተራቸው ሕዝብን መፍራት ይጀምራሉ፡፡ ሕዝቡ ምን ያደርገን ይሆን የሚለው ፍርሃት ወጥሮ ይይዛቸዋል፡፡ ሕዘቡም ተቆጥቷል፤ ተርቧል፡፡ ቁጣ ሲፈላ ደግሞ ወደ ጭካኔ ጥላቻ፤እና ምሬት ይዞራል፡፡ ርሃብ ደግሞ ሰውነት ማቅጨጭና ማደከም ብቻ ሳይሆን ሕሊናንም ያስታል፡፡ የተራበ ሰው ቁጡ ነው፡፡ጨቋኝ ገዢዎችም በፍርሃት የሚርዱት ይህን የመጨረሻውን የጨዋታ ሂደት በማንበብ ነው፡፡

ወቅቱ የለውጥነት ነው፡፡ በዚህ ፈታኝ ወቅት የኢትዮጵያ ምሁራን በጎን ቆሞ ተመልካችነትን ሊይዙ ጨርሶ አይገባቸውም፡፡‹‹የበጋ ወታደሮችና የጸሃይ መውጫ ጀግኖች›› (የድል አጥብያ አርበኞች) ሊሆኑ አይችሉም፡፡ የነጻነት፤የዴሞክራሲና የሰብአዊ መብት አድናቂዎችም ሊሆኑ አይገባቸውም፡፡ ቶማስ ፔይን እንዳለው፡አሁን ጀምሮ ከጨቋኝ ገዢዎች ጋር የሚደረገው ትግል አካል ሊሆኑ የግድ ነው እንጂ ኋላ ላይ የስልጣን ተጋሪ ለመሆን ሩጫ ውስጥ ሊፈናጠጡ አይገባም፡፡ከሕዝቡ ጋር አሁን መሰለፍ እንጂ ሲረፍድ ተቀላቅሎ በህዝቡ ላይ መቆም አይችሉም፡፡

የኢትዮጵያ ምሁራን እውቀታቸውንና ልምዳቸውን የሰውን የጭካኔ አገዛዝ ብቻ ሳይሆን፤የረሃብን፤የበሽታን፤የመሃይምነትን፤የድህነትን፤ጭለማና እጦት ለማስወገድም ለጥሩና ከትግሉ ጎራ ሆነው ሊንቀሳቀሱ ተገቢ ነው፡፡ ጭቆናና ግላዊ የበላይነት በሁሉም መልኩ ሊገታ ይገባል፡፡ የችጋርንና የድርቅን ዱካ ማጥፋት የእርሻ ምሁራን ተግባር ነው፡፡የ ኢትዮጵያ የትምህርት ስርአት በሁሉም መልኩ የወረደና ያዘቀጠ ሆኖ ሕዝቡን ሁሉ አስመርሯል፡፡ ይህን የበሰበሰና የአዘቀጠ የትምህርት ስርአት ምሁራን በመለወጥ የሕዝቡን ተስፋ ሊያለመልሙት የግድ ነው፡፡ በተለያየ የጤንነት አቅጣጫ ኢትዮጵያ አናሳ ሁኔታ ያላት ናት፡፡ ሕክምናን ከሚተገብሩት ባለሙያዎች ውስጥ በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት የህክምና ባለሙያዎች በቺካጎ ያሉት ቁጥር በብዙ ይበልጣል፡፡በዲያስፖራው ያሉ የህክምና ባለሙያዎችስ ተሰባስበው በሃገራችንና በሕዝቡ ላይ በሽታ የሚያደርሰውን ሰቆቃ ሊታገሉትስ አይገባም? በሁሉም መስክ የተሰማሩ ኢትዮጵያውያን በሃጋራችን ያለውን ችግር በየሙያ ዘርፋቸው በመሰለፍ ታገሉትና ድራሹን ሊያጠፉትስ አይገባም? ስለዚህም ሁላችንም በአንድ ጎራ ተሰልፈን ይህን ጭቆናና ግፍ በሁሉም መስክ ለመታገልና ሃገራችንና ሕዘቡንም ነጻ ለማውጣት እንነሳ!

በየሙያ መስኩ መጻፍና መናገር የጉዞው መጀመርያ ነው፡፡ የኢትዮጵያን ምሁራንና ባለሙያዎች ሕዝባዊ ምሁራበንና ባለሙያዎች እንዲሆኑ አብክሬ እለምናለሁ፡፡ ኢንተርኔት በህብረተሰቡ መሃል ብቻ ፤በጉልበተኛ ገዢዎች መሃል ብቻ ሳይሆን በምሁራንና እውቀት በራቃቸውም መሃል ሁሉንም እኩል የሚያሰልፍ እየሆነ ነው፡፡ ምሁራኑ የእውቀት ባለቤቶችና የግጭት የጥላቻ የትእግስት አልባነት ጠንሳሾች ሁለቱም ወገኖች የህዝብን ልብ በማግኘት አስተሳሰቡን የመቀየር እኩል መብት አላቸው፡፡ የኢትዮጵያ ምሁራን በመሰባሰብ የጠበበውን የእውቀት ድልድይ በማስፋት ህብረትን በማጠንከርና አንድነትን በማስተግበር ኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ ከፈላጭ ቆራጭ ገዚዎች ስርአት ወደ ዴሞክራሲያዊ ስርአት የምትሸጋገርበትን መንገድ መቀየስና ሕዝቡንም መምራት ይጠበቅባቸዋል፡፡

ጆርጅ በርናርድ ሾው የተባለው ምሁር እንዳለው ‹‹ከአሳማዎች ጋር ትግል አትግጠም ያጠነቡሃል፤ እነሱ ግን ያን ያፈቅሩታል››ማንም ህልምን ፈርቶ ሳይተኛ እደማያድር ሁሉ፤ሊደርስብኝ ይችላል ብሎ ከሚፈራው አንዳንድ አስተያየቶች ወይም ያላዋቂ ሳሚ ግለሰባዊነትን አፍቃሪዎች አፍ ፍራቻና ሽሽት ማድረግ ከሚገባውና ነው ብሎ ከሚያምንበት አስተሳሰቡ ተቆጥቦ ሕዝባዊ ተሳትፎውን ሊገታ አይገባውም፡፡በሁሉም አቅጣጫ የኢትዮጵያ ምሁራንና የሙያ በላቤቶች ይህን የወቅቱን ፈታኝ ጥያቄ መመለስ ይጠበቅባቸዋል፡፡

(ይህን ጦማር ለሌሎችም ያካፍሉ::)

ካሁን በፊት የቀረቡ የጸሃፊው ጦማሮችን  ለማግኘት እዚህ ይጫኑ::

http://www.ecadforum.com/Amharic/archives/category/al-mariam-amharic

http://ethioforum.org/?cat=24

Leave a Reply