ለአዲስ አበባ አንባቢዎቼ ለጓደኞቼ ለደጋፊዎቼ ለአዲስ አበባ ወጣቶች እና ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ወንድሞቼ እና እህቶቼ:
ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ለያንዳንዳችሁ በግል የምፅፍላችሁ ደብዳቤ ነው ብላችሁ ተገንዘቡልኝ። ይህን መልክት የማስተላልፍላችሁ ምክንያት ትልቅ ዉለታ ለመጠየቅ ነው ።
በ እ.ኤ.አ. ሰኔ 23, 2018 መስቀል አደባባይ በሚደረገው ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የህዝብ ሰላማዊ ሰልፍ እኔ መገኘት ስለማልችል በኔ ስም ተገኝታችሁ መልክቴን ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ አንድታደርሱለኝ ነው።
ከናንተ ወንድሞቸና አህቶቼ ጋር ሆኘ ድጋፌን ለትቅላይ ሚንስትሩ መልካም መሪነት ብገልፅ እንዴት ደስ ባለኝ ነበር። ግን ጊዜው አልፈቀደም ።
እንደምታውቁት ላለፉት አስራ ሶስት አመታት ለናንተ ድምፅ ሆኘ ለዓለም ህዝብ ስለ ስቃያቹና ምሬታችሁ በየሳምንቱ አንድ ሳላዛንፍ ሳስረዳሳተምር ቆይቻለሁ።
እያንዳንዳችሁ — ፅሁፌን ያነበባችሁ ቃለ መጠይቀን ያደመጣችሁ በኢትዮጵያ ሰባዊ መብት ጉዳይ የፖልቲካ እስረኞች መፈታት ጉዳይ መልካም አስተዳደር ጉዳይ እንዲሁም ስልጣን አላግባብ ለሀያምስት ዓመት ስያጎድሉ ለኖሩት እውነቱን በመናገር ለምታቁኝ ሁሉ — በ እ.ኤ.አ. ሰኔ 23, 2018 መስቀል አደባባይ ወጣችሁ እኔን ወክላችሁ የእኔ ድምፅ እንድትሆኑለኝና መልእክቴን ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ እንድትሰጡልኝ በትህትና እጠይቃለሁ ።
መልክተም ይህ ነው ።
ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩልኝ – ላሎት የሰላም የእርቅና የፍቅር በጠቅላላ አነጋገር ኢትዮጵአዊነት ለሚያደርጉት ጥረትና ልፋት ከጎኖ አጠገቦ እገኛለሁ ሙሉ በሙሉ ድጋፌን እስጦታለሁ።
ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩልኝ – ላንዴም ለዘላለምም በኢትዮጵያ የዘር የጎሳ የመከፋፈያ ፖለቲካን ከኢትዮጵያ ምድር ለማጥፋት አብሬዎት እቆማለሁ ።
ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩልኝ – ከርሶ ጋር ማንዴላ መልካምነትና እርቅ የሚባል መንገድ የሰየመልንን ይዤ አብረዎት እጉአዛለሁ።
ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩልኝ – ሰውነታችንና አንድነታችን ጥላቻንና ዘርነትን ያሸንፋል የሚለዉን እምነቶን ሙሉ በሙሉ እካፈላለሁ።
ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩልኝ – መልካሙ መፅሐፍ እንደሚለው “ጠላቶቻችን ባንድ መንገድ ይመጡብናል ግን በሰባት መንገድ ከፊታቺን ይበተናሉ።”
ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩልኝ – ከመንደር አንስተን ከትንሽ እስከ ትልቅ ከተማ እስከ ሰፊ አካባቢ የሰላምና የእርቅ ዘመቻ እናካሂዳለን ። በራሳችን ጉልበትና እግዚአብሔር በሚሰጠን ማለቂያ የሌለው ኃይል የሰላምና የእርቅ ዘመቻ እናካሂዳለን ።
ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩልኝ – ይምጡ ይከተሉን ወፊት በአንድነት ኃይል በአንድ ኢትዮጵያዊነት ጠንካራ መንፈስ ስንራመድ ።
ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩልኝ – ያቺ ኢትዮጵያ መሬት ላይ ወድቃ የተጨፈለቀች እውነት ለትንሣኤ ደርሳለች ።
ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩልኝ – የጋናው ፕሬዚደንት ቅዋሜ ንክሩማ ላፍሪካ አንድነት ድርጅት ያሉትን እደግምሎታለሁ “የኢትዮጵያ ትንሣኤ እየደረሰ ነው።”
ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩልኝ – ከርሶ ጋር ሆነን ያቺ ዉድ ኢትዮጵያ የምትባለዋን አገር በኮረብታው ላይ ለመገንባት ዝገጁ ነን ። በሷም መንገዶች ላይ ፍትህ እኩልነት ሰባዊ መብት የሕግ በላይነት እንደጎርፍ ዉሃና እንደ ታላቅ ወንዝ ይፈስባታል ።
አስታውሱ እንዳትረሱ ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩለኝ — እንወዶታለን ፍቅር ሁሉን ያሸነፋል!
እባካችሁ እባካችሁ ወገኖቼ በ እ.ኤ.አ. ሰኔ 23, 2018 መስቀል አደባባይ ወጣችሁ የእኔ ድምፅ ሁኑልኝ።
የናንተው
ዓለማየሁ
ኢትዮጵያዊነት ዛሬ
ኢትዮጵያዊነት ነገ
ኢትዮጵያዊነት ለዘላአም !

Professor Alemayehu G. Mariam teaches political science at California State University, San Bernardino. His teaching areas include American constitutional law, civil rights law, judicial process, American and California state governments, and African politics. He has published two volumes on American constitutional law, including American Constitutional Law: Structures and Process (1994) and American Constitutional Law: Civil Liberties and Civil Rights (1998). He is the Senior Editor of the International Journal of Ethiopian Studies, a leading scholarly journal on Ethiopia. For the last several years, Prof. Mariam has written weekly web commentaries on Ethiopian human rights and African issues that are widely read online. He played a central advocacy role in the passage of H.R. 2003 (Ethiopia Democracy and Accountability Act of 2007) in the House of Representatives in 2007. Prof. Mariam practices in the areas of criminal defense and civil litigation. In 1998, he argued a major case in the California Supreme Court involving the right against self-incrimination in People v. Peevy, 17 Cal. 4th 1184, which helped clarify longstanding Miranda rights issues in criminal procedure in California. For several years, Prof. Mariam had a weekly public channel public affairs television show in Southern California called “In the Public Interest”. Prof. Mariam received his Ph.D. from the University of Minnesota in 1984, and his J.D. from the University of Maryland in 1988.
ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩልኝ – ላሎት የሰላም የእርቅና የፍቅር በጠቅላላ አነጋገር ኢትዮጵአዊነት ለሚያደርጉት ጥረትና ልፋት ከጎኖ አጠገቦ እገኛለሁ ሙሉ በሙሉ ድጋፌን እስጦታለሁ።
ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩልኝ – ላንዴም ለዘላለምም በኢትዮጵያ የዘር የጎሳ የመከፋፈያ ፖለቲካን ከኢትዮጵያ ምድር ለማጥፋት አብሬዎት እቆማለሁ ።
ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩልኝ – ከርሶ ጋር ማንዴላ መልካምነትና እርቅ የሚባል መንገድ የሰየመልንን ይዤ አብረዎት እጉአዛለሁ።
ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩልኝ – ሰውነታችንና አንድነታችን ጥላቻንና ዘርነትን ያሸንፋል የሚለዉን እምነቶን ሙሉ በሙሉ እካፈላለሁ።
ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩልኝ – መልካሙ መፅሐፍ እንደሚለው “ጠላቶቻችን ባንድ መንገድ ይመጡብናል ግን በሰባት መንገድ ከፊታቺን ይበተናሉ።”
ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩልኝ – ከመንደር አንስተን ከትንሽ እስከ ትልቅ ከተማ እስከ ሰፊ አካባቢ የሰላምና የእርቅ ዘመቻ እናካሂዳለን ። በራሳችን ጉልበትና እግዚአብሔር በሚሰጠን ማለቂያ የሌለው ኃይል የሰላምና የእርቅ ዘመቻ እናካሂዳለን ።
ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩልኝ – ይምጡ ይከተሉን ወፊት በአንድነት ኃይል በአንድ ኢትዮጵያዊነት ጠንካራ መንፈስ ስንራመድ ።
ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩልኝ – ያቺ ኢትዮጵያ መሬት ላይ ወድቃ የተጨፈለቀች እውነት ለትንሣኤ ደርሳለች ።
ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩልኝ – የጋናው ፕሬዚደንት ቅዋሜ ንክሩማ ላፍሪካ አንድነት ድርጅት ያሉትን እደግምሎታለሁ “የኢትዮጵያ ትንሣኤ እየደረሰ ነው።”
ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩልኝ – ከርሶ ጋር ሆነን ያቺ ዉድ ኢትዮጵያ የምትባለዋን አገር በኮረብታው ላይ ለመገንባት ዝገጁ ነን ። በሷም መንገዶች ላይ ፍትህ እኩልነት ሰባዊ መብት የሕግ በላይነት እንደጎርፍ ዉሃና እንደ ታላቅ ወንዝ ይፈስባታል ።
አስታውሱ እንዳትረሱ ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ ንገሩለኝ — እንወዶታለን ፍቅር ሁሉን ያሸነፋል!
እባካችሁ እባካችሁ ወገኖቼ በ እ.ኤ.አ. ሰኔ 23, 2018 መስቀል አደባባይ ወጣችሁ የእኔ ድምፅ ሁኑልኝ።
የናንተው
ዓለማየሁ
ኢትዮጵያዊነት ዛሬ
ኢትዮጵያዊነት ነገ
ኢትዮጵያዊነት ለዘላአም !
Share this: