Alemayehu G Mariam Over the past few months, I have been penning occasional commentaries in a series I called “Ethiopia’s transition from dictatorship and democracy”. In my last such commentary, I argued…
በቅርቡ በዋሽንግቶን ዲሲ በጂ8 አባላት በተካሄደው፤የምግብ ዋስትና ስብሰባ ላይ በዋሽንግቶን ነዋሪ የሆነው ቆፍጣና ወጣት ኢትዮጵያዊ ጋዜጠኛ አበበ ገላው በአዳራሹ መሃል ለመሃል ቆሞ ለፈላጭ ቆራጩ ጨካኝ ገዢ መለስ ዜናዊ “ነጣነትለተነፈገው ምግብ ትርጉም አልባ ነው” በማለት ሕዝባዊ ጩኸት አሰምቶ ነበር። እና የአበበ አስተያየት ልክ ነው?
By Alemayehu G. Mariam The New Alliance for Food Security and Nutrition At the recent 2012 G8 Food Security Summit in Washington, D.C., Abebe Gellaw, a young Washington-based Ethiopian journalist,…
መለስ ዜናዊ አምባ ገነን (ዲክታተር) ነው፤ እስክንድር ነጋ ይፈታ፤የፖለቲካ እስረኞችን ፍታ:: መለስ ዜናዊ ዲክታተር ነህ!፤ሰብአዊ ክብርን እያዋረድክ ሰዎችን ለሞት የምትዳርግ ወንጀለኛ ነህ፡፡ ነጻነታችንን እየተገፈፍን ምግብ አያስፈልገንም፡፡ ከምግብ በፊት ነጻነታችን እንፈልገዋለን፡፡ ነጻነት! ነጻነት! ነጻነት! Abebe Gellaw
Alemayehu G Mariam The Man Who Cried “Freedom!” On May 18, 2012, dictator Meles Zenawi learned a lesson he will not easily forget. In the land of free speech, he…
ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ በተካሄደው በ‹‹ ዓለም አቀፉ የኤኮኖሚ ስብሰባ ላይ›› የግፍ ገዢው የፈላጭ ቆራጩ መለስ ዜናዊ አርቲ ቡርቲ መነባንብ: …በኔ እምነት በታሪክም ሆነ በቲዎሪ የኤኮኖሚ እድገትና ዴሞክራሲ ቀጥተኛ ግንኙነትም ሆነ ተዛምዶ የላቸውም፡፡ በኔ አመለካከት፤ በኤኮኖሚ እድገት ላይ የሚያስከትለውን ጫና ገሸሽ አድርገን ዴሞክራሲ በራሱ ጥሩ ነገር ነው፡፡በኔ አመለካከት አፍሪካውያን በጣም ስብጥሮች ነን፡፡ ስለዚህም ነው ብዬ አምናለሁ በመሃላችን ያለውን ግንኙነት ሰላማዊ የሚያደርገው፡፡እነዚህን ስብጥር ሰዎች በአንድነት ለማቆየት ያለው አማራጭም ዴሞክራሲ ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ስለዚህም ዴሞክራሲን መዘርጋት ይኖርብናል: ያ ግን ለእደገት ብለን አይደለም፡፡ዴሞክራሲን መዘርጋት ያለብን ስብጥር የሆኑትን በአንድነት ለማቆየት እንድንችል ነው…
ባለፈው ሳምንት የሁዋይት ሀውስ ቤተ መንግስት ቃል አቀባይ ጄይ ካርኒ ፕሬዜዳንት ኦባማ የጋናን፤ የታንዛንያን፤የበኒን ፕሬዜዳንቶችንና መለስ ዜናዊን የስምንቱን የኤኮኖሚ ሃያላን ሃገሮች (G8) ስብሰባ ላይ በካምፕ ዴቪድ ሜሪላንድ በሜይ 19 ስለ ምግብ ዋስትና በሚካሄደው ውይይት ላይ እንዲገኙ መጋበዛቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡ የአሜሪካን መንግሥት ለዘመናት ለአፍሪካ አህጉር የምግብ እርዳት ሲያደርግ መክረሙ ይታወቃል፡፡ አሁንም በድጋሚ አፍሪካን ‹‹የመረረ የችጋር ወቅት›› ገጥሟታል ይላሉ ፕሬዜዳንት ኦባማ፡፡ ኦክስፋም በበኩሉ ከአሁኑ አስፈላጊው ሁሉ ካልተደረገ በስተቀር በመታየት ላይ ያሉ ጠቋሚ ምልክቶች ሁሉ እጅጉን ዘግናኝ የሆነ መአት እንደሚከተል ያሳያሉ ይላል፡፡ የተባበሩት መንግስታት የምግብና የእርሻ ድርጅት በበኩሉ ባስተላለፈው የድረሱ ጥሪው፤ በሳሄል ምእራብ አፍሪካ ለ800,000 በችጋሩ ለተጎዱት ረሃብተኞች መርጃ የሚሆን 70 ሚለዮን የአሜሪካን ዶላር እንደሚያስፈልግ፤አስቀድሞ ማስጠንቀቂያው መተንበዩን መሰረት አድርጎ ኢትዮጵያና ሶማልያ በጉዳቱ ወደ አዘቀዘቀው ደረጃ እንደሚወርዱም ይፋ አድርጓል፡፡ የዝናቡ አናሳ መሆንም አስፈላጊውን ምርት ስለማያስገኝ የግጦሽ መሬትንም መልሶ ስለማያለማው፤በአጠቃላዩ አካባቢም የውሃ እጦት ሌላው ችግር በመሆኑ የደቡብ ኢትዮጵያውን ክፍል በእጅጉ የሚጎዳና ሕዝቡንም ለመረረ ችጋር ከብቱንም ለእልቂት የሚዳርግ ክፉ ቀን እንደሚመጣ ይተመናል:: ይህ ደሞ በገሃድ እየታየ ያለ በመሆኑ አደጋው ከአደጋዎች ሁሉ የባሰ በሆነ መልኩ ነው፡፡ አንባቢዎቼ እንደሚያስታዉሱት ሁሉ ባለፉት ሁለታ ዓመታትና ከዚያም ባለፈ በኢትዮጵያ ስለሚከሰተው ችጋር በርካታ አስተያየቶችን አስመልክቼ ጽፌ ነበር፡፡
Alemayehu G Mariam White House spokesman Jay Carney announced last week that President Obama has invited the presidents of Ghana, Tanzania, Benin and Meles Zenawi to attend the G8 Summit…
በአራት ዓመታት ውስጥ በ420 የፍርድ ሂደት፤ ቀናት: 115 ምስከሮች ተሰምተው፤ 50,000 ገጾች ያሉት ማስረጃ ተገናዝቦ፤ 1,520 መረጃ ኤግዚህቢቶች ከተመሳከሩ፤ በህውላ ለሴራ ሊዮን በተባበሩት መንግስታት በተቋቋመው ልዩ ችሎት በቀረበበት 11 ዝርዝር ክስ ቻርልስ ቴይለር: የግፍ ጦረኛውና የቀድሞው የላይቤርያ ፕሬዝደንት: ጥፋተኛ ተብሎ ተፈርዶበታል፡፡ በሰብዊ መብት ላይ ባደረሰው ወንጀል፤ ግድያ፤ አስገድዶ መድፈር፤ ሲቪል ማህበረሰቡን አካሉን በማጉደል፤እጅ በመቁረጥ፤ ሕጻናትን በጦር ሜዳ በማሰማራት፤ የፍትወት ባርነት በማካሄድ፤ ከኖቬምበር 30, 1966 እስከ ጃንዋሪ 18, 2002 በሴራ ሊዮን ሽብር በመንዛትና በማስፋፋት ወንጀል ቻርልስ ቴይለር ተበይኖበታል፡፡ በሴራ ሊዮኑ ግጭት 50,000 ዜጎች ለሞት ተዳርገዋል ሲል የተባበሩት መንግስታት ተናግሮል፡፡ ቴይለር በጭካኔ የተሞሉትን አረመኔዎች እነ ፎዲ ሳንኮህ: ሳም ‹‹ቢንቢው›› ቦካሪን: እና ኢሳ ሴሳይን በመርዳቱና በመደገፉ፤ እንደባርያ በቁፋሮው ላይ ተሰማርተው በሚያወጡት የአልማዝ ማዕድን ሽያጭ በሚከፈለው የደም አልማዝ ገንዘብ እቅድ በማውጣት፤ የጦር ስልት በመንደፍ፤ መሣርያ በመስጠት ላደረገው የግፍና የጥፋት ትብብር ነበር የስወነጀለው፡፡ ቴይለር በሚቀጥለው ወር ላይ የፍርድ የስራት ቅጣት ውሳኔው ይሰጠዋል፡፡
